መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር በቅርቡ ለቴርሺያሪ ሆስፒታል ግንባታ የሚሆነውን ቦታ ከመንግስት በሊዝ ሊጠይቅ መሆኑ ተሰማ

መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር በቅርቡ ለቴርሺያሪ ሆስፒታል ግንባታ የሚሆነውን ቦታ ከመንግስት በሊዝ ሊጠይቅ መሆኑ በጥቅምት 8 2013 .. ቦርዱ ባደረገው ስብሰባ ላይ መወሰኑን የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ማኅተመ በቀለ ተናገሩ፡፡ በጥቅምት 1 2013 .ም በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ጎን ለጎን የቴሺያሪ ሆስፒታል ግንባታው እንቅስቃሴ መጀመሩ ቅድሚያ የሚሰጠው ሥራ በመሆኑ ለዚሁ የሚሆን የኢንጂነሪነግ ቡድን በማቋቋም ወደ ሥራ መግባቱን ገልጸዋል፡፡ ለዚህ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን የተቋቋመው ቡድን በአጭር ጊዜ አጥንቶ ለቦርዱ በማቅረብ ያስወስናል ብለው ተናግረዋል፡፡