መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር ካፒታል ለማሳደግ ውሳኔ አሳለፈ

መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር በጥቅም 1 2013 .ም ባካሄደው ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ የድርጅቱን ካፒታል በብር 518 ሚሊዮን ለማሳደግ ወሰነ፡፡ አክሲዮን ማኅበሩ ይህንን ሊወስን የቻለበትን ጉዳይ የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ዶ/ር ማኅተመ በቀለ ሲያብራሩ መቅረዝ በአይነት እና በጥራት ለየት ያሉ የጤና አገልግሎቶችን ወደ ሀገራችን በማምጣት የሕሙማንን እንግልት መቀነስ እንዲሁም በዘርፉ የጤና ቱሪዝምን በማስፋፋት ለሀገር ገቢን ማስገኘትን አስቦ የሚንቀሳቀስ ነው፡፡ አክሲዮን ማኅበሩ በመጀመሪያው ዙር ሊሠራቸው ላሰባቸው ትላልቅ ሥራዎች ማለትም የጠቅላላ ሆስፒታል ፣ የዲያግኖስቲክ ማእከል፣ የመድኃኒት እና ሕክምና እቃዎች አስመጪ እና አከፋፋይ፣ ፋርማሲዎች እንዲሁም በጤና ጥናቶች እና ምርምሮች ላይ የሚሠራ ተቋም ለማቋቋም በመታሰቡ እነዚህን ለመሥራት የሚያስፈልገውን ካፒታል ለማግኘት ከባንክ ከሚገኘው ብድር በተጨማሪ ካፒታል ማሳደጉ አስፈላጊ እና ቁልፍ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አክሲዮኑንም የሚያሳድገው ለመሥራች ባለአክሲዮኖች እና ለሕዝብ በሚያወጣቸው ተራ አክሲዮኖች ሽያች መሆኑን ተናግረዋል፡፡ በተያያዘ ዜናም እስከ ታኅሳስ 30 2013 አክሲዮን የሚገዙ ባለአክሲዮኖችን እንደ መሥራች ባለአክሲዮኖች እንዲቆጠሩ ፤ ለመሥራቾች ባለአክሲዮኖች የሚሠጠው ጥቅምም 10 በመቶ እንዲሆን መወሰኑን እንዲሁም ተቋማቱ ሥራ ሲጀምሩ ሁሉም ባለአክሲዮኖች በቅናሽ አገልግሎት እንደሚያገኙ ተናግረዋል፡፡ በመጨረሻም ሲያብራሩ ‘’እኛ የምንፈልገው ሁሉም አክሲዮን የሚገዛ በሙሉ መሥራች ባለአክሲዮን እንዲሆን ነው ’’ ያሉት የቦርዱ ሰብሳቢው ሁላችሁም እስከ ታኅሳስ 30 ድረስ ከብር 20 ሺህ ጀምራችሁ በመግዛት መሥራች ባለአክሲዮን እንድትሆኑ በማለት ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡