መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር አንደኛ መደበኛ እና አንደኛ ድንገተኛ ጉባኤው በደማቅ ሁኔታ አካሄደ

መቅረዝ የጤና አገልግሎት አክሲዮን ማኅበር እሁድ ጥቅምት 1 2013 ዓ.ም. አንደኛ መደበኛ እና አንደኛ ድንገተኛ ጉባኤውን በኢንተር ኮንቲኔንታል አዲስ ሆቴል አካሄዷል፡፡ በጉባኤውም ላይ ሼር ከገዙ ባለአክሲዮኖች 72 በመቶው በራሳቸው እና በተወካያቸው ተገኝተዋል፡፡ በቅርቡ በጤና ጥበቃ ባወጣው መመሪያ መሠረት በአንድ ቦታ ለስብሰባ መገኘት የሚችለው ሰው ከ 50 በታች መሆን ስላለበት በጉባኤውም ላይ በአጠቃላይ 45 የሚሆኑ ባለአክሲዮኖች ተገኛተዋል፡፡ በጉባኤውም ላይ የሚከተሉት አጀንዳዎች ከጸደቁ በኋላ በምልዓተ ጉባኤው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡ አጀንዳዎቹም

የአንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች

  1. የ1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ አጀንዳዎች ማጽደቅ
  2. የአ/ማኅበሩን የምሥረታ ሪፖርት መስማት እና ማጽደቅ
  3. የ2013 በጀት ዓመትን የትኩረት አቅጣጫዎችን መገምገም እና ማጽደቅ
  4. የውጪ ኦዲተር መሠየም እና ክፍያውን መወሰን
  5. የመሥራች አባላትን ጥቅም መወሰን
  6. የቦርድ አባላትን ክፍያና ጥቅም መወሰን
  7. የዳይሬክተሮች ቦርድ ባለአክሲዮኖችን በመወከል በሰነዶች ማረጋገጫ መ/ቤት ተገኝተው ቃለ ጉባኤውን እንዲፈርሙ ውክልና ስለመስጠት
  8. የ1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ ቃለ ጉባኤውን ማጽደቅ

የአንደኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች

  1. የ1ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ አጀንዳዎች ማጽደቅ
  2. የአክሲዮን ማኅበሩን ካፒታል ማሳደግ
  3. የዳይሬክተሮች ቦርድ አዳዲስ የሚገቡ፣ የሚያዛውሩ እና አክሲዮን የሚያሳድጉ ባለአክሲዮኖችን በመወከል በሰነዶች ማረጋገጫ መ/ቤት ተገኝተው እንዲፈርሙ ውክልና ስለመስጠት
  4. አዲስ ባለአክሲዮኖችን እንደ መሥራች አባልነት እንዲመዘገቡ ማኅበሩ የሚቀበልበትን የጊዜ ገደብ መወሰን
  5. የ1ኛ ድንገተኛ ጠቅላላ ጉባኤ ቃለጉባኤ ማጽደቅ

ከላይ በተቀመጡት አጀንዳዎች ላይ ሰፊና ጥልቅ ውይይት ከተካሄደ በኋላ ቦርዱ ያቀረባቸውን የውሳኔ ሃሳቦች በሙሉ ድምጽ ያለምንም ተቃውሞ በማጽደቅ ጠቅላላ ጉባኤው ከ ቀኑ 11፡30 ተጠናቋል፡፡